tg-me.com/nibab_lehiwot/166
Last Update:
የእኔ ታሪክ ምዕራፍ -2
ክፍል ዘጠኝ
የሕዝቅኤል ሚስት ኤልሳ ወደ ቤቷ ስትመለስ ብቻዋን አልነበረም ከ አንድ ትልቅ እንግዳ ጋ ነበር ። በተለይ ሕዝቅኤልን በጣም ሊያስደነግጥ ከሚችል እንግዳ ጋ......... ከዛ በፊት ቪቪያን እና ሕዝቅኤል ስለወንድሟ ጉዳይ ተነጋግረው ጨርሰዋል። አብረው ሊሄዱ ወስነው ጉዳዩን ዘግተውታል።
ሕዝቅኤል ወደቤት ሲገባ ኤልሳን መጥታ ስላገኛት የናፍቆቱን ካቀፋት በኋላ ቤት ውስጥ ሌላ እንግዳ እንዳለ ተመለከተ። ፊቷን ሲያየው ድንገት ልቡ ድንግጥ አለ። የሚያውቀው ግን የረሳው ፊት.......የት ነበር ማውቃት ..... ብቻ ግን ፈራት ሴትዮዋ ከተቀመጠችበት እየተነሳች ፈገግ አለች ጭራሽ ስትስቅ ደነገጠ ማን ነች??? አለ ለራሱ የሚያውቃት የልጅነት ጓደኛው ሜሮን ነች። እሷን በመርሳቱ ራሱን ታዘበው ሜሪ አላት በማመን እና ባለማመን ውስጥ ሆኖ ሕዝቄ አለችው ፈገግታዋ ከፊቷ ሳይጠፋ.....ለ ረጅም ደቂቃወች ተቃቀፉ ከብዙ አመታት በኋላ ....... ሕዝቅኤል የልጅነቱን ሕይወት አስታወሰ እንደአዲስ የሆነ መሰለው ። ተቀምጠው ትንሽ ካወሩ በኋላ ኤልሳ እንዴት እንዳገኘቻት ነገረችው። (የሔደችው የእውነትም እናቷን አሟት ሳይሆን ሜሮን እና ጓደኞቿን ፍለጋ ነበር በጅምር የቀረውን የሕዝቅኤልን ታሪክ ለመጨረስ........
ሜሮን ካቆመበት ትቀጥለዋለች። ከዛ በኋላ ግን ምን ተፈጠረ ደህና ሆንሽ? ማቲስ ተገኘ? አብርሽስ ደህና ነው? ልጆችስ ወለድሽ? ሕዝቅኤል የጥያቄ መዓት አወረደባት።
ያኔ ልጄን ካጣሁ በኋላ ለብዙ ሳምንታት መንቃት አልቻልኩም ነበር ። ነገር ግን በህልሜ ይሁን በእውኔ ባላውቅም አንድ ሰው እየመጣ እጄን እየያዘ ያለቅስ ነበር። ይቅርታ አድርጊልኝ ሲል ይሰማኛል። ሜሮን ንቂ እባክሽ ተይ እንደዚህ አታድርጊ ይለኛል። ባለቤቴ እንዳልሆነ ግልፅ ነበር።
አንድ ቀን ግን እንዲህ አለ ሜሪ ዛሬ አይንሽን ገልጠሽ ልነግርሽ ያልቻልኩትን ይዤው የምኖረውን ሕመሜን እነግርሻለሁ። እኔ ቤት ውስጥ ምንም ያልጎደለብኝ ልጅ ነኝ ። ግን ፍቅር ጎድሎብኝ ነበር። በጓደኛቼ ተሰድቤያለሁ፣ ተንቄያለሁ፣ በቤተሰቦቼ ተፈጥሮ ምክኒያት የሰወች ማላገጫ ሆኛለሁ። ልጅነቴን እንደ ልጅ አላደግኩም ሲያሾፉብኝ፣ ከልጆች ጋ በተጣላሁ ቁጥር የእግረ አጭር ልጅ እያሉ ሲያሳምሙኝ፣ አባትህኮ እግሩ አንካሳ ነው ሲሉኝ ህመሜን ዋጥ አድርጌው ኖሬያለሁ። ወንድ ልጅ አያለቅስም ሲሉ ታውቂያለሻ ማንም እንዳያየኝ እየተደበቅኩ ደም እንባ አፍስሻለሁ። ያኔ ግን ማንም ዞር ብሎ አላየኝም ቤተሰቦቼም ቢሆኑ ......ልጅ ነበርኩ ፍቅር ያስፈልገኝ ነበር። ግን አጣሁት በእነሱ አልፈርድም ምክኒያቱም ሳዝን አይተውኝ አያውቁማ.....በቃ ራሴን በሙዚቃ ውስጥ ሸፈንኩት። ማንም እንደማይወደኝ ደመደምኩ እኔም ራሴ ራሴን ጠላሁት ። የነበረኝ አማራጭ ራሴን ከሰወች ማራቅ እና ከፍ ከፍ አድርጎ መታየት ነበር። ግን እውነታው እንደ እኔ ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚያይ አለመኖሩ ነው።
በተቀየርኩ ሰዓት መጣሽ ከራስሽም በላይ ትወጅኝ ነበር ። ምን ነበር ያኔ ልጅነቴ ሳይበረዝ ወደ እኔ ብትመጭ የምወደውን ማንነቴን ሳላጣው ባገኝሽ። ግን እድለ ቢስ ነኝ። እኔ ያላገኘሁትን ፍቅር ለ አንቺ ከየት አምጥቼ ልስጥሽ? የፈለግኩት ከቤተሰቦቼ፣ ከጓደኞቼ ፣ ከማህበረሰቡ ያጣሁትን ፍቅር አንቺ ጋ ማግኘት ነበር። ሁልጊዜ እንድትንከባከቢኝ፣ እስከ ፍፃሜ ድረስ ምንም ባደርግሽ እንዳትተይኝ፣ ከእኔ ውጭ ሌላ ሰው ጋ መኖር እንዳትችይ.......ብቻ በጣም ብዙ ነገር ከአንቺ ፈለግኩኝ በምላሹ ግን እኔ ለአንቺ ምንም መስጠት አልፈልግም።ምክኒያቱም ፍቅር ለ እኔ ሽንፈት ነው። ተሸናፊ መሆን ደግሞ አልፈልግም አንዴ ራሴን ከፍ አድርጌ ሰቅየዋለሁ።ለዛም ነው እንደማፈቅርሽ ለ አንቺ እንደተሸነፍኩ አውጥቼ መናገር የማልችለው እና ፍቅሬን ደብቄ መኖርን የመረጥኩት።
አንቺ ግን ግልፅ ነበርሽ።እብድ ነህ በይኝ አወ እብድ ነኝ ያ ጥሩ የነበረ ነገር ግን ማህበረሰቡ ያሳበደው እብድ......ብቻ ሁሉም አለፈ አንቺም ትተሽኝ ሔድሽ እንደምትመለሽ በሙሉ ልቤ አምኜ እጠብቅሽ ነበር። ግን አግብተሽ ተመለስሽ.....እኔኮ ራስ ወዳድ ነኝ ጭራሽ ከባልሽ ተፋቺ እና እኔ ጋ ሁኚ አልኩሽ። አሁን ሁሉንም ተይው ዛሬ እንደተሸነፍኩ ልመንልሽ በሙሉ ልቤ ከማንም በላይ አፈቅርሻለሁ ሜሪ ይሔው ተነሽ ስሚኝ እኔ ጉረኛው ማቲያስ በጣም አፈቅርሻለሁ!!!!! ማቲ ሲያለቅስ የሲቃ ድምፁን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰማሁት ግን አይኖቼ መገለጥ አልቻሉም እንባዬ ብቻ ፈሰሰ ማቲ እንደነቃሁ ገባው መሰለኝ ግንባሬን ስሞኝ ተሰወረ። ወዲያው ዶክተሮቹ ተከታትለው ገቡ።.........
ይቀጥላል...........
@nibab_lehiwot
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/166